Search

ዳያስፖራዎች 50 ቢሊዮን ብር ብድር ተዘጋጅቷል ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

ሰኞ ነሐሴ 26, 2017 31

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዳያስፖራ ማኀበረሰብ ብድር አገልግሎት የሚውል 50 ቢሊዮን ብር ማዘጋጀቱን አስታወቀ፡፡
በባንኩ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ የተመራው ልዑክ በዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ የተለያዩ ከተሞች የሥራ ጉብኝት በማድረግ በዚያ ከሚገኙ የዳያስፖራ ማኀበር አካላት ጋር ሰፊ ውይይት አድርጓል።
ባንኩ ለኢቢሲ በላከው መረጃ እንዳመላከተው፤ በውይይቱም ለዳያስፖራው ማኀበረሰብ ለኢንቨስትመንት እንዲሁም ለቤት እና መኪና ግዥ የሚውል 50 ቢሊዮን ብር ብድር ባንኩ ማዘጋጀቱን ተገልጿል።
የዳያስፖራውን ማኀበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርግበት አሰራር ባንኩ ከጀመራቸው ሰፊ የለውጥ ሥራዎች መካከል አንዱ መሆኑ ተመላክቷል።
 
በሜሮን ንብረት