Search

በሐዋላ ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ የሚላከው ገንዘብ በሚፈለገው ልክ ለምን አላደገም?

ማክሰኞ ነሐሴ 27, 2017 40

በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እስከ 30 ቢሊየን ብር ድረስ ሕጋዊ ሐዋላን ተጠቅመው ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ የመላክ አቅም ቢኖራቸውም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 6.9 ቢሊየን ብር ብቻ በሐዋላ ወደ ኢትዮጵያ መላኩን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ ገለፁ።

በአቶ አቤ ሳኖ የተመራ የልዑካን ቡድን ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመከላከል በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ  ከሚገኙ የዳያስፖራ አባላት ጋር ውይይት አድርጓል።

ከውጭ ከሚላከው ገንዘብ ውስጥ 78 በመቶ በሕገ ወጥ መንገድ እንደሚተላለፍ በጥናት መረጋገጡን የባንኩ ፕሬዚዳንት ለኢቢሲ ተናግረዋል።

በመንግሥት አሰራር መሰረት የውጭ ምንዛሬ ክምችት እየጨመረ ቢሄድም በሕጋዊ መንገድ ከውጭ የሚላከው ግን አነስተኛ እንደሆነ ተጠቁሟል።

በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሚገኙ ሕገወጥ የገንዘብ አስተላላፊዎች ለዚህ ችግር ዋነኛ ተዋናይ እንደሆኑም ነው አቤ ሳኖ የተናገሩት።

ለቀጣይም በዱባይ ከሚገኙ ሕጋዊ የገንዘብ አስተላላፊዎች ጋር በጋራ ለመስራት ከስምምነት ላይ መደረሱን አስታውቀዋል።

ሕገወጥ ተግባሩን ለመከላከል ዜጎች በሕጋዊ መንገድ ገንዘባቸውን መላክ እንዳለባቸውም መልዕክት አስተላልፈዋል።

 

በላሉ ኢታላ

 #EBC  #ebcdotstream  #nationalbank