Search

5ኛው የኦሮሚያ የቱሪዝም ሳምንት መካሄድ ጀመረ

ማክሰኞ መስከረም 20, 2018 61

የኦሮሚያ የቱሪዝም ሳምንት በአዲስ አበባ በስካይላይት ሆቴል ከዛሬ መስከረም 20 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ3 ተከታታይ ቀናት በተለያዩ ሁነቶች መካሄድ ጀምሯል።

መርኃ ግብሩን የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ኃላፊ አብዱላዚዝ ዳውድ (ዶ/ር) አስጀምረውታል። 

ለ5ኛ ጊዜ በሚካሄደው የቱሪዝም ሳምንት በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎች እና ባህላዊ ትውፊቶችን የሚያስተዋውቁ አውደ-ርዕዮች ቀርበዋል።

በቱሪዝም ሳምንቱ የተለያዩ የውይይት መድረኮች፣ የኦሮሚያ ቱሪዝም ሽልማት፣ የቁንጅና ውድድር እና ሌሎች መሰናዶዎች ይካሄዳሉ ተብሏል።

በሞላ ዓለማየሁ

#EBC #ebcdotstream #Irreecha #Tourism