ኢሬቻ ፈጣሪ ክረምቱን ከመጥፎ ነገሮች ጠብቆ በሰላም አሻገረን በማለት የሚከበር የምስጋና በዓል መሆኑን ከኢቢሲ ጋር ቆይታ ያደረጉት አባገዳዎች እና ሀደ ሲንቄዎች ተናግረዋል።
ኢሬቻ በመተሳሰብ መንፈስ የሚከበር በመሆኑ የተጣሉ ሰዎች በአጋጣሚ በዓሉ የሚከበርበት ስፍራ ላይ ቢገናኙ እንኳን ታርቀው በጋራ የሚያከብሩት በዓል መሆኑን አንስተዋል።

ኢሬቻ አንድነትን የሚያንፀባርቅ በዓል ነው ያሉት አባገዳዎች እና ሀደ ሲንቄዎች፤ በዓሉ የርስ በርስ ትስስርን በማጠናከር አብሮነትን ለማጉላት ከፍተኛ ሚና እንደአለው ገልጸዋል።
ኢሬቻ ሁሉም ዜጋ ያለምንም ልዩነት የሚሳተፍበት የፍቅር በዓል መሆኑንም አመላክተዋል።

የአሁኑ ትውልድ እንደ ኢሬቻ ያሉ ማኅበራዊ እሴቶችን መጠበቅ እና ማሳደግ ይገባዋል ብለዋል።
በቢታኒያ ሲሳይ