ኢትዮጵያ የውጪውን ዓለም እያማተርን ሳትሆን ያላትን እምቅ ሀብት በማስተባበር ከኋላ ቀርነትን የምናላቅቃት ባለፀጋ ሀገር ናት ሲሉ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የፕሬዚዳት ጽ/ቤት ኃላፊ እና የፐብሊክ አድሚኒስትሬሸን እና ማኔጅመንት ምሁር የሆኑት አየለ አዳቶ ገለፁ።
አንድነትን መሰረት ያደረገ ጠንካራ ሥራ ከድህነት ለመውጣት ወሳኝ መንገድ መሆኑንም ነው ያነሱት።

በቅርብ ያየናቸው የሕዳሴ ግድብ ፣ የተፈጥሮ ጋዝ ምርት እና የተለያዩ ግዙፍ የልማት ሥራዎች እንዲሁም ወደብን የተመለከቱ እና ተስፋ ሰጪ ለውጦች ኢትዮጵያን በመደመር መንፈስ ውጤታማ ማድረግ እንደሚቻል ያሳዩ ናቸው ብለዋል።
በመደመር መንግሥት መፅሐፍ እንደሰፈረው ፈጠራን በማስፋፋት ፣ በአግባቡ ጊዜን በመጠቀም እና ወደ እድገት ጎዳና በቀጥታ በመቀላቀል የኢትዮጵያን ልማት ማቀላጠፍ ይገባል ሲሉ አስረድተዋል።
ለዚህም ሁሉም ዜጋ ለጋራ ሰላም እና እድገት በትጋት ሊሰራ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በሴራን ታደሰ
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: