Search

በቢሾፍቱ ከተማ ከንቲባ አቶ አለማየሁ አሠፋ የተመራ ልዑክ በባህር ዳር ከተማ የልምድ ልውውጥ እያደረገ ነው

ሰኞ ጥቅምት 03, 2018 242

በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አለማየሁ አሠፋ የተመራ የልዑካን ቡድን በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የተሠሩ የልማት ሥራዎችን እየጎበኘ ነው።
የልዑካን ቡድኑ የባህር ዳር ከተማ የአንድ መሶብ አገልግሎት ማዕከል፣ የጣና ዳር መናፈሻ የኮሪደር የልማት ሥራዎች እና የውስጥ ለውጥስ አስፓልት መንገዶች እንዲሁም የተለያዩ የልማት ሥራዎችን በመጎብኘት የልምድ ልውውጡ ተካሂዷል።
የልምድ ልውውጡ የሁለቱን ከተሞች ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፋጠን ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል።
 
በተስፋሁን ደስታ