Search

የኢትዮጵያ ዓመታዊ የስንዴ ምርት 33 ሚሊዮን ቶን በመድረስ በአፍሪካ የመሪነት ደረጃ መያዙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ

ቅዳሜ ሰኔ 13, 2018 24

ኢትዮጵያ በዓመት 33 ሚሊዮን ቶን ስንዴ ማምረት መቻሏንና ይህም ቀደም ሲል በአፍሪካ ቀዳሚ የነበረችውን የግብፅን 9.7 ሚሊዮን ቶን ምርት በሶስት እጥፍ የሚበልጥ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (/) አስታወቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፉት ስድስት ዓመታትበስንዴ ራሳችንን መቻል አለብንሲባል ጉዳዩ እንደ ቅዠት ይታይ እንደነበር አስታውሰው፣ ዛሬ ግን በተግባር ትልቅ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።

May be an image of dais

ከዚህ በተጨማሪም በኮንስትራክሽን ዘርፍ የቢሾፍቱ ኤርፖርት ግንባታን በምሳሌነት አንስተው፣ እያንዳንዱ ዶዘር እና ማሽነሪ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የታገዘ የጥራት ቁጥጥር እያደረገ እንደሚሰራና ይህም የሰው ልጅ ሱፐርቪዥን ሳይፈልግ ጊዜና ገንዘብ እየቆጠበ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በመከላከያ ዘርፍም ሀገራችን የድሮን ቴክኖሎጂዎችን ከመጠቀም ባለፈ በስፋት ማምረት መጀመሯንና ወደ ውጭ በመሸጥ ላይ መሆኗን ይፋ አድርገዋል።

እነዚህ በስንዴ፣ በከተማ ኮሪደር ልማት፣ በኤአይ ዩኒቨርሲቲ እና በመሶብ  የተመዘገቡ ስኬቶች ኢትዮጵያን በአፍሪካ የምርታማነትና የብልጽግና ተምሳሌት እያደረጓት መሆኑ ተገልጿል።