Search

አዳጊ ሀገራትን የሚጠቅም ፍትሐዊ የፋይናንስ ሥርዓት ሊኖር ይገባል፡- የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ

ሓሙስ ጥቅምት 06, 2018 111

የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ከዓለም ባንክ እና ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዓመታዊ ጉባዔ ጎን ለጎን በ114ኛው ኢንተርገቨርንመንታል የቡድን 24 ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል።
በወቅቱም ሚኒስትሩ አዳጊ ሀገራት ትክክለኛ ድምፅ እና በቂ ሃብት እንዲያገኙ ብዝኀነት ያለው ዓለም አቀፍ ፍትሐዊ ሥርዓት ሊኖር ይገባል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ለአዳጊ ሀገራት ኢኮኖሚ ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ እንዲሁም ለረጅም ጊዜ ልማት የሚያገለግል ፍትሐዊ የፋይናንስ አቅርቦት አስፈላጊነት መሆኑንም አጽንዖት ሰጥተዋል።
በተለይም የተጠናከረ የገንዘብ ድጋፍ እና ትብብር ወሳኝ መሆናቸውን አመላክተዋል።
 
በጌትነት ተስፋማርያም