Search

የልማት ሥራዎችን በፍጥነት በማጠናቀቅ የኅብረተሰቡን ኑሮ ይበልጥ ማሻሻል ይገባል - ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ

እሑድ ጥቅምት 09, 2018 34

የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በክልሉ በመገንባት ላይ ያሉ፣ የተጠናቀቁ እና አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።
የርዕሰ መስተዳድሩ የመስክ ምልከታ የገጠር ኮሪደሮችን፣ የቅርስ ጥበቃ ሥራዎችን፣ የመንገድ ፕሮጀክቶችን፣ የመንገድ ዳር መብራቶችን፣ ሼዶችን፣ የሌማት ትሩፋት እንቅስቃሴዎችን እና የመናኸሪያ አገልግሎት መስጫ ስፍራ ግንባታዎችን ያካተተ ነው።
በወቅቱ አቶ ኦርዲን በድሪ፤ የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።
 
የተጀመሩ የልማት ሥራዎች በፍጥነት መጠናቀቅ አለባቸው ያሉት አቶ ኦርዲን በድሪ፤ ፕሮጀክቶችን በተቻለ ፍጥነት ወደ ሥራ በማስገባት የኅብረተሰቡ ተጠቃሚነት ማሳደግ ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።
 
በቴዎድሮስ ታደሰ