Search

ትውልድ ነቅቶ ከመባላት በመውጣት ሃብቱን ማልማትና ከልመና መውጣት ይገባዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ሰኞ ጥቅምት 10, 2018 35

ትውልድ ልመናን እየተቀባበለ መሄድ የለበትም የሚል ፅኑ እምነት ይዘን ፀጋዎቻችንን በማልማት ሀገርን ወደ ብልጽግና ለማሸጋገር እየሠራን ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
"ኢትዮጵያ በባሌ ምድር ያለውን የተፈጥሮ ፀጋ ይዛ ለምን ለማኝ ሆነች የሚለውን ጥያቄ መመለስ አልቻልኩም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያውያን ከኋላ ጋር ያለን ፀብ ወደፊት መራመድ እንዳንችል በእጅጉ ይዞናል፤ ወደኋላ ማየት ያለብን ለትምህርት ብቻ መሆን አለበት ብለዋል፡፡
ትውልድ ነቅቶ፣ ከመባላት ወጥቶ፣ በባሌ ያለውን የተፈጥሮ ሃብት አልምቶ ከልመና እንዲወጣ የሁላችንም ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አሳስበዋል፡፡
ሶፍ ኡመርን የመሰለ ሃብት እስካሁን አለመልማቱ ትልቅ ቁጭት እንደፈጠረባቸው የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ብዙ እምቅ ፀጋዎች ያሏት ሀገር ናት ብለዋል፡፡
"ሀገር በአንድ ትውልድ አይሠራም፤ አንድ ትውልድ ጀምሮም አይጨርሰውም፤ ሀገር የሚሰራው በትውልድ ቅብብሎሽ ነው" ሲሉም ተናግረዋል።
 
በላሉ ኢታላ