Search

ኢትዮጵያ እና የሳዑዲ የልማት ፈንድ በወሳኝ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ አጋርነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

ማክሰኞ ጥቅምት 11, 2018 69

የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ከዓለም ባንክ እና ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ዓመታዊ ጉባኤ ጎን ለጎን ከሳዑዲ የልማት ፈንድ ዋና ኃላፊ ሱልጣን አብዱራህማን አል-ማርሻድ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።

በኢትዮጵያ እና በሳዑዲ ዓረቢያ መካከል ጠንካራ እና እያደገ የመጣ የልማት አጋርነት መፈጠሩ በውይይቱ ላይ ተነሥቷል።

አቶ አሕመድ ሽዴ የሳዑዲ የልማት ፈንድ ኢትዮጵያ ለምታደርጋቸው የልማት ጥረቶች ለሚያደርገው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።

ሁለቱ ሀገራት ቅድሚያ በሚሰጧቸው የጋራ ኢኮሚያዊ ጉዳዮች ላይም ትብብርን የበለጠ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ፤ በተለይም አዲሱንዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግዙፍ ፕሮጀክት ጨምሮ ኢትዮጵያ በኢነርጂ እናመሠረተ ልማት ዘርፎች ትልቅ ኢንቨስትመንት እንደሚያስፈልጋት አበክረው አስታውቀዋል።

ሱልጣን አብዱልራህማን አል-ማርሻድ በበኩላቸው፣ የሳዑዲ የልማት ፈንድ ሁለቱ ሀገራት ቅድሚያ በሚሰጧቸው የጋራ ፕሮጀክቶች ላይ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ይህ ድጋፍ ከኢትዮጵያ ዘላቂ የልማት አጀንዳዎች ጋር በሚጣጣም መልኩ የሚደረግ መሆኑንም ነው ያስታወቁት።

በዮናስ በድሉ

#EBC #ebcdotstream #Ethiopia #SaudiArabia #SFD