Search

በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ እና በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠሩ ከባድ መኪኖች በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ተዋወቁ

ማክሰኞ ጥቅምት 11, 2018 79

ይህን ያስተዋወቁት ቢአኤካ ግሩፕ እና የቻይናው የከባድ መኪና አምራች ኩባንያ ሻክማን በጋራ በመሆን ነው።

በመድረኩ ተሽከርካሪዎቹ ለኢትዮጵያ ገበያ ከዛሬ ጀምሮ ክፍት የተደረጉ ሲሆን፤ የቻይና መንግሥት እና የሻንሺ ግዛት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የሻክማን ኩባንያ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

ይህ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሆነ የኢነርጅ ሽግግርን የሚያመጣ ቁልፍ ጅማሮ ተደርጎ የሚወሰድ መሆኑ የተነገረ ሲሆን፤ በቀጣይም በአማራጭ ኃይል እንዲሁም በታዳሽ ኃይል የሚንቀሳቀሱ ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ ገበያ በስፋት ይገባሉ ተብሏል።

በብሩክታዊት አስራት

#ebcdotstream #ethiopia #lngvehicles #electricvehicles #china