Search

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በበጋ ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ

ሓሙስ ኅዳር 04, 2018 101

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ እና የ2018 በጀት ዓመት የበጋ ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሂዷል።
‎በመድረኩም በክረምት ወራት የተከናወነው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳትፎ በበጋ ወራትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር ጥሪ አቅርበዋል።
 
የክልሉ ሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ አለምነሽ ይባስ በበኩላቸው፤ በክልሉ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ364 ሺ በላይ ሰዎችን በማሳተፍ ከ937 ሺ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደቻለ ተናግረዋል።
የአቅመ ደካሞችን ቤት ማደስ፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ፣ የማዕድ ማጋራትን ጨምሮ በ14 የተለያዩ ዘርፎች የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራ ሲከናወን መቆየቱን ጠቅሰው፤ በበጋ ወቅትም የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶቹ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አመላክተዋል።
በነስረዲን ሀሚድ