Search

ዳዊት መለሰን የሚጠብቁ ዛሬ ያገኙታል

ዓርብ ኅዳር 05, 2018 574

ተወዳጁ ድምጻዊ ዳዊት መለሰ 23 ዓመታት በኋላ 'ምስጢር' የተሰኘውን የአልበም ስራውን በዛሬው ዕለት በዲጂታል መንገድ ለአድማጮቹ እንደሚያደርስ አሳውቋል።

ድምጻዊ ዳዊት መለሰ 1959 . በአዲስ አበባ ነው የተወለደው። በፈለገ ዮርዳኖስ፣ በጥቁር አንበሳ እና ቦሌ የተማረው ዳዊት፤ ከሮሃ ባንድ ጋር በፕሮፌሽናል የሙዚቃ ባለሙያነት ነው ዋናውን የሙዚቃ ሕይወት የጀመረው።

1976 . በደርግ ዘመን በኪነት በአማተርነት ደረጃ ወደ ሙዚቃው ዓለም ሲቀላቀል ከእንግሊዘኛ ዘፋኝነት በተጨማሪ ድራም ይጫወት ነበር። በተለይም የማይክል ጃክሰን ዘፈኖችን አድናቂና የዘፈን ሕይወቱ ማሟሻ ሥራም የእርሱ ነበር።

በዘፋኝነት ሙያ ውስጥ (ፕሮፌሽናል) ሆኖ መሥራት እንደሚፈልግ ለአባቱ ሲነግር 'ዘፋኝነቱ ላይ በርታበት ነገር ግን ትምህርትህን አትርሳ' ብለውት እንደነበር ያስታውሳል

በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት በተጋባዥነት ይጫወት የነበረው ዳዊት በሮሃ ባንድ ውስጥ ከመሐሙድ አህመድ፣ ከኩኩ ሰብስቤ፣ ከነዋይ ደበበ እና ከተክሌ ተስፋዝጊ ጋር ሆኖ በእንግሊዘኛ ብቻ ይጫወት ነበር።

ከአማርኛ ዘፈኖች ውስጥ 'ሴት አላምንም' እና 'ገዳም' ለመጀመሪያ ጊዜ በአማርኛ የተጫወታቸው ዘፈኖቹ ናቸው። 

1983 የመጀመሪያ አልበሙ የሆነው 'አልቻልኩም' ሙሉ በሙሉ በአበበ መለሰ ግጥምና ዜማ ደራሲነት፤ በሮሃ ባንድ አጃቢነት ለአድማጭ አድርሷል። በጊዜው በሀገሪቱ በነበረው ወቅታዊ ሁኔታ አልበሙ እምብዛም የመደመጥ ዕድል ባያገኝም ለየት ያለ የአዘፋፈን ስልቱ ግን ሙዚቃ ወዳጆች ልብ ውስጥ አስቀምጦታል።

በዚህ አልበም የተካተቱት 'ይበራል ልቤ' 'ነጋ ነጋ' እና 'አልቻልኩም' የተሰኙት ሥራዎች አድማጩን በፍቅር የጣሉ ነበሩ። ዳዊት ከባህላዊ የአዘፋፈን ስልት የራቁና በጊዜው አፈንጋጭ የመሰሉ አዳዲስ ጣዕም ያላቸው ስራዎችን ይዞ መቀላቀሉም የዘመናዊ ሙዚቃ የሽግግር ዘመን ምሳሌ ተደርገው ከሚጠቀሱ ጥቂት ድምጻውያን አንዱ አድርጎታል።

በዘመኑ የግርማ በየነን 'ሴት አላምንም' ዘፈን አስፈቅዶ የተጫወተ ምናልባትም የመጀመሪያው ድምጻዊም ሳይሆን እንደማይቀር የነገርለታል፡፡

'ፍቅር በሎተሪ' የተሰኘው ሁለተኛ አልበሙን የያዘ ካሴት 1987 . ሲያወጣ ተቀባይነት ማግኘት ብቻም ሳይሆን የመጀመሪያ አልበሙም ቀስ በቀስ እንዲደመጥ ምክንያት ሆነ።

ከተመስገን ተካ ጋርፍቅር በሎተሪእናአትመኪበት ጨምሮ ዝነኛ ሥራዎችን አብረው ሰርተዋል። በተለይምፍቅር በሎተሪ‘  ዓመት የፈጀ ስራው ነበር። ሁለተኛው አልበም አገር ቤት ቢቀረጽም ጥራቱ ጥሩ ስላልሆነ አሜሪካ ለእረፍት በሄደበት ወቅት ነው ዳግም ተቀርጾ የተሰራው። በወቅቱ አበጋዝ፣  ሄኖክ እና ፋሲል ጥሩ ቅጂ ሆኖ እንዲቀረፅ አድርገውለታል። በሲዲ እና በካሴት የታተመ ሥራው ሲሆን፤ የካሴቱ አልበም 10 ሥራ ሲኖረው ሲዲው ላይ 11 ዘፈኖች አሉት። ከአሥራ አንዱ ሥራዎች አንዱም 'Sally' የተሰኘ የእንግሊዝኛ ዘፈን ነው።

1992 'አንቺን ነው' ብሎ በሶስተኛ አልበም ወደአድማጭ የተመለሰው ድምጻዊው፤ በተለይ 'አይሰማሽም' እጅግ ከፍ ያለ ተቀባይነት ያገኘበት ስራው ሆኖ አልፏል። በተለያየ ጊዜ ከሌሎች ድምጻውያን ጋር በጋራ ባወጣቸው የአልበም ስራዎች ውስጥም የተወደዱ ስራዎቹን ለአድናቂዎቹ አድርሷል።

'አንድ ቀን' የተሰኘውን አራተኛውና የመጨረሻ የአልበም ስራው 1995 . ለአድማጮች ያደረሰው ድምጻዊ ዳዊት፤ የአልበሙ መጠሪያ በሆነው ዘፈን 'አይቀርም አንድ ቀን' እንዳለው በመጨረሻ ከረጅም ጊዜ ጥበቃና ናፍቆት በኋላ በሙሉ የአልበም ስራ ሊደመጥ ለዓርብ ህዳርአመሻሽ ቀን ቆርጧል።

የዳዊት መለሰ አዲሱ 'ምስጢር' የተሰኘውና በራሱ የዩትዩብ ገጽ የሚለቀቀው፤ 11 የሙዚቃ ስራዎችን የያዘው አምስተኛ የአልበም ስራው፤ የዘፈን ስብስብ ብቻ ሳይሆን 20 ዓመታትን የፈጀ 'ታሪክ' እንደሆነ ጠቅሷል።

 

 

አክሱማዊት ገብረሕይወት

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ:

ተያያዥ ዜናዎች: