ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በኢትዮጵያ በይፋዊ የሥራ ጉብኝት ላይ የሚገኙት የቱርክዬ ፕሬዚዳንት ረጀብ ጠይፕ ኤርዶዋን ዛሬ በአዲስ አበባ የሁለትዮሽ ውይይት ካደረጉ በኋላ የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
ፕሬዚዳንት ኤርዶዋን በመግለጫቸው፥ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የመጀመሪያው የእስልምና መዳረሻ እና የፍትሐዊው ንጉሥ ነጃሺ መገኛ መሆኗ ለሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መጠናከር ትልቅ መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በእስልምና ታሪክ ያላት የላቀ ሚና ለቱርክዬ ሁሌም ትልቅ ትርጉም እንዳለው ፕሬዚዳንቱ አንስተው፤ ይህ ጥንታዊ እና ታሪካዊ ወዳጅነት ዛሬም በልማት እና በዲፕሎማሲያዊ ትብብር ደምቆ መቀጠሉን አክለዋል።

የቱርክዬ የልማት ትብብር ኤጀንሲ (TIKA) ታሪካዊውን የንጉሥ ነጃሺ መስጂድ እና የንጉሡን መካነ መቃብር ዕድሳት ማጠናቀቁን ጠቅሰው፤ ይህም የሁለቱን ሀገራት እና ሕዝቦች ታሪካዊ ትስስር ይበልጥ እንደሚያጠናክረው ተናግረዋል።
የቱርክዬ ማሪፍ ፋውንዴሽንም በሀገራቸው እና በኢትዮጵያ መካከል የትምህርትና የባህል ድልድይ በመሆን የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች ይበልጥ የማቀራረብ ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ፕሬዚዳንት ኤርዶዋን በመግለጫቸው አረጋግጠዋል።
በላሉ ኢታላ
#Ethiopia #Turkiye #Diplomacy #History #KingNajashi #RecepTayyipErdoğan #EthiopianBroadcastingCorporation #EBC #EBCdotstream