Search

አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) የሹመት ደብዳቤያቸውን ለፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኡመር ጌሌህ አቀረቡ

ሰኞ ኅዳር 08, 2018 130

በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (/) የሹመት ደብዳቤያቸውን ለሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢስማኤልመር ጌሌህ አቅርበዋል።

አምባሳደሩ በዚሁ ወቅት፥ በጅቡቲ በሚኖራቸው የሥራ ቆይታ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ስትራቴጂያዊ ግንኙነት ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሠሩ ተናግረዋል።

ቀጣናዊ ትስስርን ለማጎልበት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እንዲሁም ሰላም እና መረጋጋት እንዲፀና ለማስቻል በትኩረት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

በተጨማሪም የሁለቱን ሀገራት ትብብር ከፍ ወዳለ ደረጃ ለማድረስ እንዲሁም የጋራ እሴቶችን ለማጎልበት ያላቸውን ቁርጠኝነት መግለጻቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

#ebcdotstream #ethiopia #djibouti #diplomacy