Search

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በጋሞ ዞን በደረሰው አደጋ የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ

ሰኞ መጋቢት 07, 2018 64

የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡና ለተጎዱ ዜጎች የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (/) ባስተላለፉት የሐዘን መግለጫ መልዕክት፣ለኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ልባዊ መጽናናትን ተመኝተዋል።

ፕሬዝዳንቱ በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦችና በጉዳቱ ለተጎዱ ወገኖች ሁሉ ያላቸውን ጥልቅ ስሜትና አጋርነት ገልጸዋል።

ሶማሊያ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ጎን በጽናት እንደምትቆምም ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ አረጋግጠዋል።

#EthiopianBroadcastingCorporation #Ethiopia #Somalia #Solidarity #Landslide