Search

በዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጮች የሚያስተዋውቅ የቢዝነስ መድረክ ተካሄደ

ሓሙስ ሰኔ 18, 2018 52

ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢፌዴሪ ኤምባሲ እና በአሜሪካ የንግድ ምክር ቤት የአሜሪካ-አፍሪካ የቢዝነስ ማዕከል ትብብር የተዘጋጀ የኢንቨስትመንት ማስተዋወቂያ መድረክ ተካሂዷል።

በንግድ ምክር ቤቱ ጽሕፈት ቤት በተካሄደው በዚህ መድረክ ላይ በርካታ ታዋቂ የአሜሪካ ኩባንያዎች ኃላፊዎች እና የቢዝነስ ተወካዮች ተሳትፈዋል።

በመድረኩ ላይ በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልእክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱዓለም በኢትዮጵያ ለግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት ያሉትን ምቹ ሁኔታዎች እና ሰፊ ዕድሎች በዝርዝር አቅርበዋል።

የአሜሪካ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ አምባሳደር ብናልፍ ጥሪ ማቅረባቸውን በዋሽንግተን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።