የሸዋል ወር ጨረቃ ዛሬ ባለመታየቷ 1447ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል ከነገ ወዲያ አርብ መጋቢት 11 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከበር ተገልጿል።
የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ሸህ ሙባረክ መሐመድ አወል ለኢቢሲ ዶትስትሪም እንደገለፁት፤ የሸዋል ወር ጨረቃ ዛሬ ባለመታየቷ 1447ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል ከነገ በስቲያ መጋቢት 11 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከበር አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት 1447ኛውን የኢድ አል ፊጥር በዓል አስመልክቶ ቀድሞ ብሎ ባስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፤ ሕዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር ስለ ሀገር ሰላምና መረጋጋት ፈጣሪን በመማጸን እንዲሁም እስልምና ባዘዘው መሠረት በታላቅ ጨዋነትና ሥነ-ምግባር ሊሆን እንደሚገባም አሳስቧል።
በላሉ ኢታላ
#EBC #Ethiopia #EidAlFitr1447 #IslamicCouncil #Shawwal #Ramadan2026 #EidMubarak