የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እየጎለበተ መምጣቱን ያሳየ ነው ሲል የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ።
የጋራ ምክር ቤቱ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።
የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ በለጠ ሲጌቦ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምርጫው ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሚጠበቅበትን ተወጥቷል።
ለምርጫው በስኬት መካሄድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን አቶ በለጠ ተናግረዋል።
ምርጫው የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀገርና ህዝብን ያስቀደሙበት እንዲሁም የህዝቡ የነቃ ተሳትፎ ጎልቶ የታየበት ነው ብለዋል።
አጠቃላይ የምርጫው ሂደት በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እየጎለበተ መምጣቱን ያሳየ መሆኑን አመልክተዋል።
የምርጫው ሂደት ሰላማዊና ነጻ ሆኖ መጠናቀቁንም አስታውቀዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።