ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ከሆኑት ንስቲያን ክርስተንሰን ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል።
ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ “በመጪው መስከረም በኢትዮጵያ በሚካሄደው የኖርዲክ - አፍሪካ ኢቪ ሰሚት (Nordic Africa EV Summit) ላይ በጋራ በምንሰራቸው ጉዳዮች ላይ ከአምባሳደሩ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገናል” ብለዋል።
ከተማችን አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ኩነቶችን የማስተናገድ እና በብቃት የመወጣት ልምድ ያካበተች እና ተመራጭ እየሆነች የመጣች በመሆኗ ይህንንም ጉባኤ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እናሳካዋለን ሲሉም አክለዋል።