Search

የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል - ከውድቀት ወደ ዳግም ትንሣኤ

ቅዳሜ ሰኔ 13, 2018 61

ሀገራችን በቀይ ባሕር ቀጣና የነበራትን ጂኦ-ፖለቲካዊ እና የንግድ መስመር ደኅንነት ለማስጠበቅ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል፣ በዘመኑ ከነበሩት የአፍሪካ የባሕር ኃይሎች እጅግ ዘመናዊ እና ተወዳዳሪ ተቋም ነበር።

የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል 1946 . በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በዘመናዊ መልክ ተመሠረተ። የዚህ ኃይል ምሥረታ የተፋጠነው ታዲያ የቀይ ባሕር ጠረፎችን (ምጽዋን እና አሰብን) መጠበቅ የግድ በመሆኑ ነው።

No photo description available.

ባሕር ኃይላችን የምጽዋ ባሕር ኃይል አካዳሚን በማቋቋም ከእንግሊዝ ሮያል ኔቪ፣ ኖርዌይ እና አሜሪካ ጋር በመተባበር መኮንኖችን በከፍተኛ ዲሲፕሊን ያሠለጥን ነበር።

በደርግ ዘመን የባሕር ኃይሉ ይበልጥ እየተጠናከረ ሄደ። ባሕር ኃይላችን በወቅቱ ዘመናዊ የጥበቃ መርከቦች፣ ፈጣን አጥቂ ጀልባዎች፣ የባሕር ላይ ፈንጂ አምካኝ መርከቦች እና ከሶቭየት ኅብረት የተገኙ የሚሳኤል ተሸካሚ ጀልባዎች ባለቤትም ነበር።

ይሁን እንጂ በሰሜን የሀገራችን ክፍል ጦርነቱ እየተባባሰ በመምጣቱ፣ ሠራዊቱ መደበኛ ጥበቃውን ትቶ የሕይወት መሥዋዕትነት የጠየቁ ከባድ ውጊያዎችን በቀይ ባሕር ጠረፎች ላይ ለማድረግ ተገዷል።

1983 የፖለቲካ ለውጥ እና የባሕር በር ማጣት በኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ላይ ያደረሰው ጉዳት ከፊል ሳይሆን ሁለንተናዊ እና አውዳሚ ነበር። የባሕር ኃይል ያለ ባሕር በር ሊኖር ስለማይችል፣ ሠራዊቱ ታሪካዊ መሠረቱን አጣ።

1982 . ምጽዋ፣ እንዲሁም 1983 . አሰብ በሻዕቢያ ቁጥጥር ሥር ሲውሉ፣ የባሕር ኃይሉ የጦር መርከቦች ማቆሚያዎቹን፣ የጥገና ዶኮችን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ መልካም ስም የነበረውን የምጽዋ ባሕር ኃይል አካዳሚን አጣ።

በከፍተኛ ወጪ እና ጥረት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገራት (እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ሩሲያ) የሠለጠኑት የባሕር ኃይል አባላት ተበተኑ። ይህ ውድቀት እጅግ ውድ የሆነ የሀገር ሀብት ብክነትን ያስከተለ ከመሆኑም በላይ፣ በባሕር ኃይሉ አባላት እና በሕዝቡ ሥነ-ልቦና ላይ ጥልቅ የኀዘን እና የቁጭት ጠባሳ ጥሏል።

የባሕር በር ከተዘጋ በኋላ፣ ከጦርነቱ የተረፉት የጦር መርከቦች የገዛ ሀገራቸውን ውኃ ለቅቀው ወደ የመን፣ ጅቡቲ እና ሳዑዲ ዓረቢያ ወደቦች ለመሰደድ ተገደዱ።

በወቅቱ ሠራዊቱ በመበተኑ እና በጀቱም በመቋረጡ ምክንያት፣ መርከቦቹ የቆሙበትን ከፍተኛ የወደብ ኪራይ በውጭ ምንዛሪ መክፈል አልተቻለም።

በዚህም የተነሣ በአስተናጋጅ ሀገራቱ መርከቦቹ በዝገት እንዲበላሹ ተደርገው፣ በመጨረሻም በጨረታ ለብረታብረትነት እንዲሸጡ ሆነዋል።

የባሕር ኃይል ዳግም ምሥረታ እና የዲፕሎማሲ ጥረቶች

ምንም እንኳን ታሪካዊው ሠራዊት ቢፈርስም፣ የአካዳሚው ምሩቃን በሀገራችን የባሕር ትራንስፖርት ዘርፍ ትልቅ ዐሻራ ጥለው አልፈዋል።

በቅርብ ዓመታት ደግሞ ኢትዮጵያ ይህን ታሪካዊ ስህተት ለማረም እና ጂኦ-ፖለቲካዊ ተጽዕኖዋን ለመመለስ ወሳኝ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምራለች።

ሀገራችን 2011 . የባሕር ኃይሏን በይፋ መልሳ አቋቁማለች።

አዲሱ የባሕር ኃይል በተግባር ሉዓላዊነትን ለማስከበር የባሕር በር የግድ ይለዋል። ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት መርሕ ላይ በተመሠረተ ዲፕሎማሲ የባሕር በር ለማግኘት ሰፊ ጥረት እያደረገች ነው።

May be an image of text

የኢትዮጵያ የባሕር ኃይል ታሪክ የውድቀት ብቻ ሳይሆን የትንሣኤም ታሪክ ነው። ይህ የሠራዊቱ ትንሣኤ ከወታደራዊ አደረጃጀትም በላይ በርካታ ታሪካዊ ትርጉሞችን የያዘ ነው፦

በተቋሙ መፍረስ ምክንያት በቀድሞ የባሕር ኃይል አባላትም ሆነ በኢትዮጵያውያን ሥነ-ልቦና ውስጥ ተፈጥሮ የነበረውን ጥልቅ ስብራት የሚጠግን እና የሀገርን የተገፈፈ ኩራት ዳግም የሚመልስ ነው።

በምጽዋ አካዳሚ ተቀርጾ የነበረውን ጥብቅ ወታደራዊ ዲሲፕሊን እና በቀይ ባሕር ቀጣና የነበረውን የደኅንነት ዘብነት ራዕይ በአዲስ ትውልድ ከዳር የሚያደርስ ነው።

የባሕር ኃይላችን ዳግም መቋቋም የኢትዮጵያን ስትራቴጂያዊ ሕልውና የሚያረጋግጥ እና የቀድሞውን የባሕር ላይ ገናናነታችንን በአዲስ ሞራል፣ በአዲስ አቅም እና ራዕይ ዳግም ሕያው ያደረገ ታሪካዊ ትንሣኤ ነው።