Search

ፈረንሳይ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈች

ሓሙስ ሰኔ 18, 2018 55

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን አጠቃላይ ምርጫ ይፋዊ ውጤት ማሳወቁን ተከትሎ የፈረንሳይ መንግሥት ለምርጫው ስኬታማነት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል።

የፈረንሳይ መንግሥት በመልዕክቱ አዲስ የተመረጡ የፓርላማ አባላትን፣ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናትን እንዲሁም በሂደቱ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላትን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እና የሲቪክ ማኅበራትን ለስኬቱ አድንቋል፡፡

ከሁሉም በላይ ደግሞ ምርጫውን ስኬታማ በሆነ መንገድ ላከናወነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቱን ማስተላለፉን ከፈረንሳይ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።