በአሜሪካዋ ሜምፊስ ከተማ የሐረሪ ባህልና ስፖርት ፌስቲቫል የከተማዋ በዓል ሆኖ እንዲከበር የከተማው ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ መወሰኑ ተገለጸ።
በከተማዋ የሚኖሩ የሐረሪ ማኅበረሰብ በየዓመቱ የሚያከብሩት የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል አከባበር ዕውቅና ማግኘቱ ባህሎቻቸውን፣ ታሪኮቻቸውንና እሴቶቻቸውን ለሌላው ማኅበረሰብ በላቀ ደረጃ ለማስተዋወቅ እንደሚያስችል ተጠቅሷል።
ዕውቅናው በተለያዩ ዓለማት ለሚገኙ የሐረሪ ማኅበረሰብ ትልቅ ኩራት ከመሆኑም ባሻገር ጥንታዊ ባህሎቻቸውን ጠብቀው ለማቆየትና ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል።
የከተማዋ ምክር ቤት የሰጠው እውቅናም ከተማዋ ለባህል ብዝኃነት፣ ለሕዝቦች የእርስ በእርስ ትውውቅና ትስስር እንዲጠናከር ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ተመላክቷል።
እንዲሁም በሜምፊስና በሐረር ከተሞች መካከል የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ተጠቁሟል።
በዓሉ በየዓመቱ በፈረንጆቹ ጁላይ 1 ቀን እንዲከበር ምክር ቤት በአዋጅ መደንገጉም ተገልጿል።