Search

የዘንድሮው የፕሪሚየር ሊጉ አሸናፊ ሲዳማ ቡና ዋንጫውን ተረከበ

እሑድ ሰኔ 28, 2018 73

2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በይፋ ተጠናቅቋል።

በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ያደረጉት ጨዋታ፣ በኢትዮ ኤሌክትሪክ 1 0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

ለኢትዮ ኤሌክትሪክ ብቸኛዋን የማሸነፊያ ግብ አቤል ሀብታሙ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።

38 ሳምንታት የሊጉ መርሐ ግብሮች 68 ነጥብ በመሰብሰብ 2018ቱን የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ያነሣው ሲዳማ ቡና፣ በቀጣዩ ዓመት በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ ኢትዮጵያን ወክሎ ተሳታፊ ይሆናል።

ዛሬም የዓመቱ ሻምፒዮን የሆነበትን የክብር ዋንጫ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ከክብር እንግዶች እጅ ተቀብሏል።

በእድሪስ አሕመድ