የአማራ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ በሚገኘው 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤ በ2019 በጀት ዓመት ለክልሉ የልማት ሥራዎች ማስፈጸሚያ በጀት 402 ቢሊዮን 285 ሚሊዮን 713 ሺህ 544 ብር ሆኖ አጽድቋል።
የ2019 በጀት ዓመት አጠቃላይ በጀቱ በ2018 በጀት ዓመት ከተመደበው የ78 ነጥብ 4 በመቶ ወይም የ176 ቢሊዮን 831 ሚሊዮን 934 ሺህ 307 ብር ዕድገት እንዳለው የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኀላፊ አታላይ ጥላሁን ገልጸዋል፡፡
ከዓመታዊ በጀቱ 71 ነጥብ 3 በመቶ የሚሆነው በክልሉ ከሚሠበሠብ ገቢ፣ 27 ነጥብ 6 በመቶ የሚሆነው ከፌዴራል መንግሥት ጥቅል የቀመር መደበኛ ድጋፍ ድርሻ እንዲሁም ቀሪው ደግሞ ከልዩ ልዩ ምንጮች እንደሚሸፈን ተገልጿል።
የተመደበው በጀት በዓመቱ ለዘላቂ ልማት ዕቅድ ማስፈጸሚያ፣ ለልዩ ልዩ ሪፎርሞች እና መዋቅራዊ ማሻሻያዎች፣ ለድህነት ተኮር ሥራዎች እና የክልሉን የመልማት አቅም ታሳቢ ያደረገ ስለመሆኑም ተመላክቷል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ በ2018 በጀት ዓመት የክልሉ መንግሥት ሥራ ላይ ላዋለው ከ39 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ የተጨማሪ በጀት አጽድቋል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: