ከስምንቱ የሥራ ቡድኖች የተውጣጡ 15 የአጀንዳ ምክረ-ሃሳብ አጠናቃሪዎች ያጠናቀሩትን የአጀንዳ ሃሳብ ለየስራ ቡድናቸው አቅርበዋል።
500 አባላት ካሏቸው ስምንት የስራ ቡድኖች ከእያንዳንዳቸው 15፣ በድምሩ 120 አባላት ያሉት ቡድን ካለፈው ሐሙስ ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም የሥራ ቡድኖች የተነሱ የአጀንዳ ምክረ-ሃሳቦችን በማዳመጥ ወጥ የሆነ ምክረ-ሃሳብ ማቅረብ የሚያስችል ሥራ ሲሰራ ቆይቷል።
የእያንዳንዱ የሥራ ቡድን ተወካዮችም የየቡድናቸውን የአጀንዳ ምክረ-ሃሳቦች ድግግሞሽ በማስወገድ፣ ያልተቀናጁ ሀሳቦችን በማደራጀት ወጥ የሆነ ሰነድ አዘጋጅተው ዛሬ ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ 500 አባላት ላሉት የሥራ ቡድን አቅርበዋል።
የተደራጁ አጀንዳዎች የቀረቡላቸው ስምንቱ የሥራ ቡድኖች ሃሳብ እና አስተያየት አክለው የመጨረሻው ሰነድ እንዲዘጋጅ ለአደራጅ ቡድኖቹ መልሰዋል።
ግብአቶችን የሰበሰቡ የአጀንዳ ምክረ-ሃሳቦችን የሚያጣጥሙ ቡድኖችም የተሰጧቸውን ሃሳቦች በነገው ጠዋት መርሃ-ግብር አካተው ለየሥራ ቡድኖቻቸው በከሰዓቱ መርሃ-ግብር በድጋሚ በማቅረብ እንደሚያፀድቁ ይጠበቃል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: