Search

የመንዙማው ባልቅኔና የቱባው ወሎ አሻራ የሸህ ሰይድ ኢብራሂም ጫሊ መንፈሳዊ፣ ሀገራዊና ጥበብ ነክ ሕያው ቅርስ

ማክሰኞ ነሐሴ 19, 2018 40

በወሎ ወረባቦ ወረዳ ከቢስቲማ 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ጫሊ፣ ከቦታዋ ስም በላይ ስሟ ጎልቶና ገዝፎ በሀገራችን በስፋት እንዲነሳ ያደረጉት ስመ ገናናው የነቢዩ ሙሐመድ (..) ማዲህ ሸህ ሰይድ ኢብራሂም ናቸው።

ማዲሁ ሸህ መሐመድ አወል በግጥማቸው "ስሙ የተጠራው ሰው ቢኖርበት ነው" ብለው እንደገለጹት ሁሉ፤ የጫሊ ምድር በየትኛውም ስፍራ በቱባነቱ እንዲታወቅ ያደረጉት የመንዙማው ባለቅኔ ሸህ ሰይድ ኢብራሂም (ሸህ ጫሊ) ናቸው።

1870ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ ከአባታቸው ሸህ ኢብራሂም ያሲን እና ከእናታቸው / ዘቡራ ሙሐመድ ተወልደው በራስ ወሌ ቤት ከእቴጌ መነን ጋር ያደጉት እኚህ ታላቅ ሊቅ፤ ፈጣን አእምሮ፣ ከፍተኛ የግጥምና የዜማ ችሎታ የነበራቸው ከመሆኑም በላይ ከአካባቢው ገዥዎችና ከጣሊያን ወራሪዎች ጋር ያደረጉት ትግል፣ እንዲሁም በርካታ የአረብኛና የአጅ ጽሑፎቻቸው ለሀገር ትልቅ አሻራ ጥለው አልፈዋል።

በኢትዮጵያ የእስልምና  ታሪክ ውስጥ የዘመናዊ ነሺዳ ቅልቅል የሌለበትን፣ አልተቀየጠም የሚባለውንና የራሱ ልዩ ቅርጽ ያለው የወሎ ቱባ መንዙማን በጥበብ ቀምረው ለአሁኑ ትውልድ ያቆዩት እኚሁ ባለቅኔ እንደሆኑ ይነገራል።

20ኛው ክፍለ ዘመን በይዘትም ሆነ በቋንቋ ልቀት እንደ እርሳቸው መንዙማን የቀመረ እንደሌለ የሚነገርላቸው ሸህ ሰይድ ኢብራሂም የታሪክ ፀሐፊው ከድር ታጁ እንደገለጹት ለክታብ ወገበ-ቀላል የነበሩ የታላቅ ድርሰት "ጋን" ነበሩ።ይላቸዋል፡፡

120 በላይ የግጥም መድብሎቻቸው መካከል በተገኙት 16 መድብሎችና 49 ጥልቅ ስንኞች ላይ ስለ ሀገር አጥብቀው ተጨንቀዋል።

በተለይምሚምያበመባል የሚታወቀው መድብላቸው በሀገር ላይ የወደቁ የዝናብ እጥረቶችን፣ ድርቅን፣ የእርስ-በርስ ጦርነቶችንና ዳግማዊ የፋሽስት ወረራን በመቃወም ለሀገር ነጻነት፣ ፍትሕና ሰላም በተደረጉ ውጤታማ ዱዓዎችና እርግማኖች የተሞላ ሲሆን፤ ይህም ከመንፈሳቸው ጋር የተጣባውን ጥልቅ ሀገር ወዳድነት ያሳያል።

ከዚህም በላይ ነጥብ የሌላቸውን የአረብኛ ፊደላት ብቻ በመጠቀምሙህመልበተባለ ረቂቅ የአጻጻፍ ስልት የጻፉት ኪታባቸው በግብፅ ሙዚየም ውስጥ የታላቅ ቅርስነት ክብር አግኝቶ ለዓለም ሕዝብ መጎብኛና የታሪክ ማጣቀሻ ሆኖ ይገኛል።

በጫሊ ምድር የተዘራው ይህ የመንፈሳዊነት፣ የጥበብና የሀገር ፍቅር አሻራ ዛሬም ድረስ የሀገራችን ኩራትና የትውልዶች መማሪያ ሆኖ ይኖራል።

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: