በሦስተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቸስተር ሲቲ በኢቲሃድ አዲስ አዳጊውን ኮቨንትሪ ሲቲ አስተናግዶ 1 ለ 0 አሸንፏል።
ኤንዞ ፈርናንዴዝ ለማንቸሰተር ሲቲ የመጀመሪያ ጨዋታውን ባደረገበት ጨዋታ፣ አንቷን ሴሜኒዮ ያቀበለውን ኳስ ተጠቅሞ ብቸኛዋን ግብ ያስቆጠረው ኤርሊንግ ሃላንድ ነው። ይህች ግብ ለሃላንድ 300ኛ የክለብ ግቡ ሆና ተመዝግባለች።
ይህ ውጤት ሦስቱንም ጨዋታዎቹን ያሸነፈውን ማንቸስተር ሲቲን በ9 ነጥብ የደረጃ ሰንጠረዡን በጊዜያዊነት እንዲመራ አድርጎታል።
ኤርሊንግ ሃላንድም ከማንቸስተር ዩናይትዱ ብሩኖ ፈርናንዴዝ እና ከሊቨርፑሉ አሌክሳንደር አይሳክ ጋር የኮከብ ግብ አግቢነት ፉክክሩን እየመራ ይገኛል።
በአራተኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ማንቸስተር ሲቲ ወደ ኦልድ ትራፎርድ አቅንቶ ማንቸስተር ዩናይትድን ይገጥማል።
አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ: