Search

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ያጋጠመ አደጋ የለም

እሑድ ነሐሴ 18, 2017 71

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ካፋ እና ኮንታ ዞኖች የመሬት መንሸራተት አደጋ ተከስቶ 10 ሰዎች ሞተዋል በሚል የተሰራጨው መረጃ ሐሰት መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገለፀ።

የክልሉ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ለማ መሰለ (ዶ/ር)፥ በክልሉ ካፋ እና ኮንታ ዞኖች በ18/12/2017  በጣለው ከባድ ዝናብ የመሬት መንሸራተት ተከስቶ የሰው  ሕይወት አልፏል በሚል የተሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ  ነው ብለዋል።

በክልሉ ለአደጋ ተጋላጭ ናቸው ተብለው በተለዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎች  አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አክለዋል።

አሁን ላይ እየጣለ ካለው ዝናብ  ጋር ተያይዞ ሊከሰት የሚችለውን አደጋ ለመከላከል ኮሚሽኑ  ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ  እየሠራ አንደሚገኝ የገለፁት ዶ/ር ለማ፤ ዜጎችም ተገቢ የሆነ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

እንደዚህ ዓይነት የውሸት መረጃዎችን የሚያሰራጩ ኃላፊነት የጎደላቸው አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባም ዶ/ር ለማ አሳስበዋል።

በሰለሞን ባረና

#ኢቢሲዶትስትሪም #ደቡብምዕራብኢትዮጵያ #ካፋ #ኮንታ