Search

የኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዚዳንት አዲስ አበባ ገቡ

ሰኞ ነሐሴ 19, 2017 41

የኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዚዳንት ፍራንሲያ ኤሌና ማርኬዝ የሀገሪቱን ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በመምራት ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ጋር አዲስ አበባ ገብተዋል።

ምክትል ፕሬዚዳንቷ ቦሌ አየር መንገድ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና  የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ  አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ምክትል ፕሬዚዳንቷ በአዲስ አበባ በሚኖራቸው ቆይታ ከተለያዩ የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮ - ኮሎምቢያ የቢዝነስ ፎረምም በነገው ዕለት በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገልጿል።

በኤዶም አማረ

#EBCdotstream #ETV #Ethiopia #Colombia