Search

ኮሎምቢያ በኢትዮጵያ ኤምባሲዋን ከፈተች

ረቡዕ ነሐሴ 21, 2017 124

ኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳን ፍራንሲያ ማርክኬዝ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጤሞቴውስ (ዶ/ር) በተገኙበት በኢትዮጵያ ኤምባሲዋን ከፍታለች።

የኤምባሲው መከፈት የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር እና ዲፕሎማሲያዊ ትብብርን ለማጎልበት ትልቅ እርምጃ ነውም መባሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያደረሰን መረጃ ያመለክታል።

ኮሎምቢያ ኤምባሲዋን 1967 በአዲስ አበባ የከፈተች ሲሆን፤ ኤምባሲው 1974 ጀምሮ ዝግ ሆኖ ቆይቶ ነበር። 

ኢትዮጵያ እና ኮሎምቢያ 1949 ጀምሮ የረጅም ጊዜ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ነበራቸው።