Search

“የልጅነት ልባቸው ታክሞ ልብ የሚያክሙ ሐኪሞች አፍርተናል"፦ ዶ/ር ዳዊት እሸቱ

ሓሙስ ነሐሴ 22, 2017 203

በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ማዕከል በሚሰጠው ነፃ የልብ ሕክምና የልጅነት ልባቸው ታክሞ  ዛሬ ላይ በተለያዩ ጤና ተቋማት ልብ የሚያክሙ የጤና ባለሞያዎች ማፍራት መቻሉን የማዕከሉ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ዶ/ር ዳዊት እሸቱ ገለፁ።

በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ማዕከል ባለፈው ዓመት ብቻ ከ 40 በላይ የሚሆኑ ሕፃናት  ወደ እስራኤል ሄደው እንዲታከሙ ማድረጉንም ነው ዶ/ር ዳዊት የገለፁት።

የአገልግሎት ስፍራዎች ለሕዝብ ግንኙነት ክፍት እንደሆኑት ሁሉ ማዕከሉ ከሰው ለሰው እንዲሁም ከታካሚ እና ሀኪም ግንኙነት ባሻገር ልብን ከልብ የሚገናኝበት ስፍራ መሆኑም ተገልጿል።

ዶ/ር ዳዊት እሸቱ በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕጻናት መርጃ ማዕከል የመጀመሪያው እና ብቸኛው ነፃ የልብ ሕክምና ማዕከል መሆኑን ገልፀው፣  ከግለሰብ አንስቶ እስከ ድርጅቶች ድረስ ሁሉም የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ እና ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

ማዕከሉ በሚሰጣቸው የነጻ የልብ ቀዶ ሕከምና አገልግሎቶች የሕጻናትን ጤና ከመመለሰ ባሻገር በሕጻናት ዕድገት እና ትምህርት ላይ አዎንታዊ አስተዋጽ በማበርከት ለቤተሰብም ከሥነ ልቦና ከማኅበራዊ እና ከኢኮኖሚያዊ ጫናዎች መታደግ ችሏል።

በሴራን ታደሰ