Search

ከጉርሻቸው ቀንሰው ለሕዳሴ ግድብ ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ የቦንድ ግዢና የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉት እናት

ዓርብ ነሐሴ 30, 2017 67

ወይዘሮ አሰለፈች ፀጋዬ ይባላሉ። ነዋሪነታቸው በሻሸመኔ አራዳ ክፍለ ከተማ መናኸሪያ አካባቢልዩ ስሙ ቡና ተራ በሚባለው ሰፈር ነው።

ወይዘሮ አሰለፈች በዚህ ሰፈር የወዳደቁ ፌስታሎችን ሰብስበው በመሸጥ እንደዚሁም ከሰል በመቸርቸርይወታቸውን ይመራሉ።

ወይዘሮ አሰለፈችታላቁ የኢትዮጵያዳሴ ግድብ ግንባታ የመሰረትንጋይ ከተጣለበት አንስቶ ደጋፍ ሲያደርጉ ቆይተዋል።

ኢትዮጵያ ታላቁ የሕዳሴ ግድብን ገድባ እንድታጠናቅቅ በውስጣቸው ከነበረው ቁጭት እና ጉጉት የተነሳ ባለፉት 14 ዓመታት በቦንድ ግዢና በድጋፍ መልክ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ማበርከታቸውን ይናገራሉ።

አሁን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ለምረቃ በመዘጋጀቱ ደስታዬ ወደር የለውም፤ እንኳን ደስ አለን ሲሉም ለመላው ኢትዮጵያውያን መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለፍፃሜ እንዲደርስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለተጫወቱት የላቀ ሚናም ወይዘሮ አሰለፈች አመስግነዋል።

አሁን ምኞቴ ታላቁ የኢትዮጵያዳሴ ግድብ የሚገኝበት ጉባ ሄጄ ምረቃውን መታደም ነው ብለዋል።

በፈቃደአብ አለማየሁ

#EBCdotstream #ETV #GERD #RenaissanceDam #ሕዳሴግድብ #Inauguration