Search

ኪን ኢትዮጵያ በሩሲያ የጥበብ ድግሱን እያቀረበ ነው

ሓሙስ መስከረም 01, 2018 64

ኪን ኢትዮጵያ የባህል እና የጥበብ መድረክ በሩሲያ የመጀመሪያውን የጥበብ ድግስ እያቀረበ ነው፡፡
የባህል ቡድኑ የጥበብ ድግሱን እየቀረበ የሚገኘዉ የባህል ማዕከል በመባል በሚታወቀዉ በሴንት ፒተርስበርግ ከተማ በሚገኘው ጥንታዊው አሌክሳንድርስኪይ ቴአትር ቤት ነዉ፡፡
በዚህ የመድረክ ትዕይንት የኢትዮጵያን ሕብረ-ብሔራዊነት የሚያንፀባርቁ ሥራዎች እየቀረቡ ይገኛል፡፡
 
የባህል እና የጥበብ ቡድኑ የመጀመሪያውን የሩሲያ ዝግጅቱን እያቀረበ ያለው ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ65 በላይ ሀገራት ተሳታፊ በሆኑበት የዓለም አቀፍ የባህል ፎረም እየተካሄደባት በምትገኘው ከተማ ላይ ነው፡፡
ይህም የኢትዮጵያን እምቅ የብዝኃ ባህሎችን እና የኪነ ጥበብ ሃብቶችን ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያን የባህል ጉዞ በዋናነት የሚያስተባብሩት የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ከሻኩራ ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር ነው፡፡
 
በፍሬው በኩረፅዮን