Search

የሩሲያውያንን ቀልብ መሳብ የቻለው ኪን ኢትዮጵያ

ቅዳሜ መስከረም 03, 2018 63

ኪን ኢትዮጵያ የባህል እና የጥበብ ቡድን በሩሲያ ሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ለሩሲያ ታዳሚያን ሕብረ ብሔራዊነትን የሚያንፀባርቁ የተለያዩ የባህል እና የኪነ-ጥበብ ሥራዎችን አቅርቧል። 

በመድረኩ የታደሙ ሩሲያዊያን የኢትዮጵያን ባህል፣ ጥበብ እና አኗኗር የሚያሳዩ ዝግጅቶች ቀልብ የሚስቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያውያንን የሙዚቃ ምቶች በመስማታቸው እና ቆንጆ የባህል አለባሳትን በማየታቸውም መደሰታቸውን ገልጸዋል።

የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማህዲ፤ ዝግጅቱ የታለመለትን ግብ መምታቱን አስታውቀዋል።

ኪን-ኢትዮጵያ ዝግጅቱን ያቀረበበት መንገድ የታዳሚውን ትኩረት የሳበ እንደነበር አንስተዋል።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳይሬክቶሬት ጀነራል የሆኑት አምባሳደር ነብዩ ተድላ በበኩላቸው፤ በመድረኩ የቀረበው ትዕይንት በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን የባህል ትስስር ያጠናክራል ብለዋል።

በሩሲያ ሴንት ፒተስበርግ የቀረበው የኪን ኢትዮጵያ ዝግጅት ለቀጣይ የፖለቲካ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች መደላድል የፈጠረ መሆኑንም ተናግረዋል።

የሻኩራ ፕሮዳክሽን ሥራ አስኪያጅ ካሙዙ ካሳ የመድረክ ዝግጅቱ ኢትዮጵያን ያስተዋወቀ መሆኑን አስረድቷል። 

ዝግጅቱ አንድነት የታየበት እና ሕዳሴ በተመረቀበት ማግስት የቀረበ በመሆኑ በእጅጉ እንዳስደሰተው ገልጿል።

በተጨማሪም የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማህዲ ከሩሲያ ባህል ፌዴሬሽን ሚኒስትር ዴኤታ ጃና አሌክሳቫ ጋር ተወያይተዋል።

በመሐመድ ፊጣሞ

#EBC #ebcdotstream