Search

በአፋር የእርሻ ልማትን በማስፋፋት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር እየተከናወነ ያለው ሥራ

ሰኞ መስከረም 19, 2018 55

ይህ ዓይነ ገብ የሆነ የሆነ ለምለም አረንጓዴ ስፍራ የሚገኘው በአፋር ክልል፣ ሀሪ-ረሱ ዞን፣ ሰሙ-ሮቢ ገለኣሉ ወረዳ ነው።

ወረዳዋ ሰሙ-ሮቢ የሚለውን ስያሜዋን ያገኘችው በአካባቢው ከሚገኘው ‘ሰሙ’ ተራራ እና ወረዳዋን አቋርጦ ከሚያልፈው ‘ሮቢ’ ወንዝ እንደሆነ በአካባቢው ማህበረሰብ ይነገራል።

ከሰሙ ተራራ ስር የምትገኘው ወረዳዋ ከሮቢ ወንዝ ውሃ እየጨለፈች ሁለ-ገብ የግብርናራን በስፋት በማከናወን ላይ ትገኛለች።

በወረዳዋመስኖ እናክረምት ዝናብ 5 ሺህ 200 በላይ ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኖ እንደሚገኝ የወረዳዋ እርሻ እና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ መሐመድ ዬሴጌሌ ለኢቲቪ ተናግረዋል።

አካባቢው ለግብርና ምቹ በመሆኑ ኅብረተሰቡን ከተረጅነት ለማውጣት መንግሥት በወረዳዋ ከትናንሽ ማሳዎች እስከ ሰፋፊእርሻ ልማቶች ላይትኩረት እየሠራ ይገኛል ብለዋል።

በወረዳዋ ማሾ፣ በቆሎ፣ ጤፍ፣ ሽንኩርት፣ ቃሪያ እና የተለያዩ ቋሚ ተክሎች እየለሙ እንደሚገኙም ነው የገለጹት።

በአፋር ክልል 2018 ምርት ዘመን በአጠቃላይ 142 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል።

በክልሉ ከፍተኛ የክረምት ዝናብ በሚያገኙት ኪልበቲ-ረሱ እና ፈንቲ-ረሱ ዞኖች ላይ የተለያዩ ሰብሎች እየለሙ ይገኛሉ።

በክልሉ በመኸር ወቅት በዘር ለመሸፈን ከታቀደው መካከል ከ40 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን መቻሉ ተገልጿል።

በመካከለኛው እና በታችኛው አዋሽ አካባቢዎች ከከፊል አርሶ አደሮች እስከ ኢንቬስተሮች በመስኖ ልማት የተለያዩ ሰብሎችን እና ለምግብነት የሚውሉ ቋሚ ተክሎችን በማልማት ላይ ናቸው።

በአጠቃላይ በክልሉ የኅብረተሰቡን የምግብ ዋስትና በማረጋገጥ ከተረጂነት ለመላቀቅ እየከናወነ ባለው ሥራ አበረታች ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑንም ነው መረጃዎች የሚያመላክቱት።

በሁሴን መሐመድ

#EBCdotstream #Afar #Agriculture

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ:

ተያያዥ ዜናዎች: