Search

ቀልጣፋ እና ዘመናዊ አገልግሎቶችን የሚሰጠው የመሶብ አንድ ማዕከል

ማክሰኞ መስከረም 20, 2018 198

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተለያዩ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ጣራ ስር በማጣመር እና ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የሚሰጥ አገልግሎት ነው።

ህብረተሰቡ ያነሳቸው የነበሩ ቅሬታዎችን ለመፍታት የተቋቋመው አገልግሎቱ የተገልጋይን ጊዜ ለመቆጠብ እና እንግልቱን ለመቀነስ ስለማስቻሉ ይነገራል።

የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ አገልግሎቱ 13 የከተማ አስተዳደር እና 3 የፌደራል ተቋማት እንዲሁም 2 ባኮች፣ በድምሩ 18 ተቋማትን የተጣመሩበት መሆኑን ገልጸዋል።

በማዕከሉ የፋይናንስ፣ ገቢዎች፣ ቤቶች ልማት፣ ትራንፖርት እና ሌሎች አገልግሎቶች የሚሰጡ ተቋማት እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ በቀጣይ የሚጨመሩ ሌሎች ተቋማት እንደሚኖሩ ነው የተናገሩት።

ማዕከሉ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ገልጸው፤ ይህም የከተማ አስተዳደሩን አገልግሎት አሰጣጥ እንደሚያቀላጥፈው እና እንደሚያዘምነው ይጠበቃል ብለዋል።

በሜሮን ንብረት

#EBCdotstream #ETV #MesobCenter #AddisMESOB #A-MESOB