Search

ከተማን በማዘመን ሥራዎቻችን በአፍሪካ ምሳሌ እየሆንን ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ሓሙስ መስከረም 22, 2018 33

በኢትዮጵያ በተሰሩ እና እየተሰሩ ባሉ ከተማን የማዘመን ሥራዎቻችን በአፍሪካ ምልክትና ምሳሌ እየሆንን ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
በከተሞቻችን ለብዙ የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ሥራ ተጀምሯል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ነገር ግን ከተሞቻችን መድረስ የሚገባቸው ቦታ ላይ ገና አልደረሱም ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ከኮሪደር ልማቱ ብዙ ሀገራት ተሞክሮ ለመውሰድ ጥያቄ እያቀረቡ መሆኑን ገልጸው፤ የጀመርነው መንገድ በጣም ውጤታማና ተስፋ ሰጪ በመሆኑ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አረጋግጠዋል።
ሀገሪቱ ራሱን የሚወድና የሚያከብር፣ መለወጥና ማደግ የሚፈልግ ህዝብና መንግስት አላት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ተባብረን እና በርትተን እንስራ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በመሀመድ ፊጣሞ