Search

ኢሬቻ የሰላም፣ የፍቅር፣ የይቅርታ እና የአብሮነት በዓል - ሃጂ አወል አርባ

ዓርብ መስከረም 23, 2018 28

የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሃጂ አወል አርባ የ2018 የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ሃጂ አወል በመልዕክታቸው፥ ኢሬቻ የሰላም፣ የፍቅር፣ የይቅርታ እና የአብሮነት በዓል መሆኑን ገልጸዋል።

በዓሉ የኦሮሞ ሕዝብ ከተቀሩት የኢትዮጵያውያ ሕዝቦች ጋር በመሆን በፍቅርና በአንድነት የሚያከብሩት በዓል መሆኑን አክለዋል።

የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል ልዩ የሚያደርገው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በህብረት ባሳካን ማግስት የምናከብረው መሆኑ ነው ብለዋል።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የአንድነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

#EBC #Irreecha #Ethiopia #ኢሬቻ