Search

ፓርላማ ቻናል መከፈት ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የራሱ ድርሻ ይኖረዋል - ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)

እሑድ መስከረም 25, 2018 25

ሕዝብና ምክር ቤቱ መረጃ የሚለዋወጡበት የኢቲቪ ፓርላማ ቻናል ለጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የራሱን ድርሻ ለመወጣት ያስችላል ሲሉ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚንስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ገለፁ።
የፓርላማ ቴሌቪዥን የምክር ቤቱን የሕግ አወጣጥ ሂደት፣ በምክር ቤቱ የሚወሰኑ ውሳኔዎችን እና የሕዝብ ውክልና ሥራዎችን አፈፃፀም ለሕዝብ ለማቅረብ አጋዥ ነው ብለዋል።
ከዚህ አኳያ ፓርላማው የራሱ ቻናል እንዲኖረው የምክር ቤቱ የበላይ አመራሮች ከፍተኛ ቁርጠኝነት ማሳየታቸውንም አንስተዋል።
ራሱን በይዘትና አቀራረብ እያዘመነ የመጣው ኢቢሲ፤ ነገ መስከረም 26 ቀን 2018 የኢቲቪ ፓርላማ ቴሌቪዠን ቻናሉን በይፋ ሥራውን ያስጀምራል።