Search

የኢቲቪ ፓርላማ ቻናል ራሱን ችሎ መከፈቱ ሕዝብ የሚደመጥበትን የዴሞክራሲ ባህል ለማሳደግ ያስችላል፡- አፈ ጉባኤ አለማየሁ ባውዲ

እሑድ መስከረም 25, 2018 34

የሕዝብ እንደራሴዎችን ሚና ለማጎልበት እና ሕዝብ የሚደመጥበትን የዴሞክራሲ ባህል ለማሳደግ የኢቢሲ ፓርላማ ቻናል መከፈት ፋይዳው የጎላ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ተናገሩ።
ሚዲያ በሕዝብ እና በመንግሥት መካከል እንደ ድልድይ ሆኖ ያገለግላል ያሉት ዋና አፈ ጉባኤው፤ የኢቲቪ ፓርላማ ቻናል በየደረጃው ለሚገኙ ምክር ቤቶች ተጨማሪ አቅም ይሆናል ብለዋል።
የዚህ ትውልድ አካል ሆነው የፓርላማ ቻናል መከፈቱ አስደስቶኛል ሲሉ ዋና አፈ ጉባኤው ተናግረዋል።
ራሱን በይዘትና አቀራረብ እያዘመነ የመጣው ኢቢሲ፤ ነገ መስከረም 26 ቀን 2018 የኢቲቪ ፓርላማ ቴሌቪዥን ቻናሉን በይፋ ሥራውን ያስጀምራል።
 
በተመስገን ተስፋዬ