Search

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ከ ጊኒ ቢሳው ይጫወታል

ረቡዕ መስከረም 28, 2018 146

በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ምድብ አንድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ የምድቡን 9 ጨዋታ ከጊኒ ቢሳው ያደርጋል።

2026 ዓለም ዋንጫ ውጭ መሆኑ ቀድሞ የተረጋገጠው ብሔራዊ ቡድኑ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በሩዋንዳ የሚያደርገው ጨዋታ ከመርሀ ግብር ማሟያነት ያለፈ ትርጉም አይኖረውም።

ከቀናት በፊት ወደ ሩዋንዳ ያመሩት ዋልያዎቹ ትላንት የመጨረሻ ልምምዳቸውን ጨዋታው በሚደረግበት አማሆሮ ስቴዲየም ሰርተዋል።

ካደረጋቸው 8 ጨዋታዎች አንዱን ብቻ ያሸነፈው ብሔራዊ ቡድኑ 6 ነጥብ 5 ደረጃ ላይ የተቀመጠ ሲሆን የዛሬ ተጋጣሚው ጊኒ ቢሳው 10 ነጥብ 4 ደረጃ ላይ ትገኛለች።

የምድቡ አሸናፊዎች በቀጥታ 2026 ዓለም ዋንጫ በሚሳተፉበት ማጣሪያ ምድቡን ግብጽ 20 ነጥብ እየመራች ሲሆን ዛሬ ቀድማ ከተሰናበተችው ጂቡቲ የምታደረገውን ጨዋታ ካሸነፈች ማለፏን ታረጋግጣለች።

በአንተነህ ሲሳይ

#ebcdotstream #ebcsport #Ethiopianationalteam #WCQ

አስተያየትዎን እዚህ ያስፍሩ:

ተያያዥ ዜናዎች: