Search

የኩታ ገጠም እርሻ ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው - የግብርና ሚኒስትር አቶ አዲሱ አረጋ

እሑድ ጥቅምት 02, 2018 29

የግብርና ሚኒስትር አቶ አዲሱ አረጋ እንዲሁም የተለያዩ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን እና በቀቤና ልዩ ወረዳ በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኘውን የበቆሎ እና የጤፍ ግብርና ልማት ጎብኝተዋል።



በዘንድሮ የመኸር እርሻ ከ20 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ተሸፍኗል ያሉት የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ ከዚህ ውስጥ12.3 ሚሊዮን የሚሆነው በኩታገጠም ክላስተር የለማ መሆኑን ገልፀዋል።



አሁን ላይ በሀገሪቱ በስፋት እየተሰራበት የሚገኘው የኩታ ገጠም እርሻ ምርታማነትን ከ30 በመቶ በላይ ማሳደግ አስችሏል ብለዋል።

በወንድወሰን አፈወርቅ

#EBC #agriculture #Ethiopia