Search

በብሔራዊ ጥቅም የማይደራደር ትውልድ መፍጠር ይገባል - አቶ መስፍን ዳኜ

ረቡዕ ጥቅምት 12, 2018 44

መልካም ታሪኮቻችን ለሀገር ግንባታ መጠቀም እና አንድነትን ተጠቅሞ ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር እንደሚገባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ መስፍን ዳኜ ገልጸዋል።
በብሔራዊ ጥቅም ላይ የማይደራደር ትውልድ መፍጠር እንደሚገባ የገለፁት አቶ መስፍን፣ በባሕር በር ጉዳይ ላይም ትኩረት ሰጥቶ ከነጣይ ትርክት ይልቅ የወል ትርክትን ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ፖለቲከኞችና ምሁራን ሀገርን አንድ በሚያደርጉ ጉዳዮች ላይ ማተኮር እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ሀገር የሚገነባው በትውልድ ቅብብሎሽ በመሆኑ የትናንት ስህተቶችን እያረሙ ለሀገር የሚመጥን አዲስ ነገር በመፍጠር ለቀጣዩ ትውልድ ትልቅ ሀገርን ማስተላለፍ እንደሚገባም ገልጸዋል።
 
በሄለን ተስፋዬ