Search

የኮይሻ ፕሮጀክት አቅምን እንዴት ወደ ጥቅም መቀየር እንደሚቻል በደንብ ያሳየ ነው፦ ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)

እሑድ ጥቅምት 16, 2018 42

የኮይሻ ፕሮጀክት አቅምን እንዴት ወደ ጥቅም መቀየር እንደሚቻል በደንብ ያሳየ ነው ሲሉ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (/) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (/) 2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮ ኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማን በኮይሻ ግድብ ከሚኒስትሮች ጋር አካሂደዋል።

/ር ኤርጎጌ፥ የኮይሻ ኘሮጀክት በአንድ ወቅት ቆሞ እንደነበር አስታውሰው፤ ነፍስ ዘርቶ አሁን ካለበት ደረጃ እንዲደርስ የተሰጠው ቁርጠኛ አመራር የሚደንቅ እንደሆነ ነው የገለጹት

ተርባይኖች ከዚህ ቀደም ከውጭ ይገዙ እንደነበር አንስተው፤ ኮይሻ ግድብ ግን ተርባይኖች በሀገር ውስጥ መመረታቸው እያደገ ያለውን የውስጥ አቅም ያሳየ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም ለግድቡ ግንባታ የሚውለው አብዛኛው ግብዓት ከአካባቢው የተገኘ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለመቀነስ ማስቻሉን ተናግረዋል።

ይህም በአግባቡ ከተገለገልንባቸው የየአካባቢውን ማኅበረሰብ ከመጥቀም አልፈው ለሀገራዊ ዕድገታችን  መሠረት የሚሆኑ ያላስተዋልናቸው በርካታ ሀብቶቻችንን እንድናይ ዓይናችንን የገለጠ ነው ብለዋል።

በሜሮን ንብረት

#ebcdotstream #ethiopia #koysha