Search

ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የተነሱ ዋና ዋና ጥያቄዎች መካከል፦

ማክሰኞ ጥቅምት 18, 2018 156

☑ ኢትዮጵያን ለማዳከም ከታሪካዊ ጠላቶች ጭምር ተልዕኮ በመቀበል የባንዳነት ተግባር ላይ የተሰማሩ ፀረ ሰላም ኃይሎች ላይ ተገቢውን እርምጃ ለመውሰድ ምን እየተሰራ ነው? ከሕዝቡስ ምን ይጠበቃል?
☑ የፕሪቶሪያውን ስምምነት ወደ ጎን በመተው የትግራይን ሕዝብ ወደ ጦርነት እና ስቃይ ለማስገባት የሚሞክረው የሕወሓት ቡድን አሁን ደግሞ ከሻዕቢያ ኃይሎች ጋር ጭምር የሀገሪቱን ሰላም ለማወክ እየሰራ በመሆኑ መንግሥት ክልሉን ሰላማዊ ለማድረግ ምን እየሰራ ነው? የክልሉ አሁናዊ የፖለቲካ፣ የሰላም እና ፀጥታ ሁኔታስ ምን ይመስላል?
☑የሀገራዊ ምክክር ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል፤ ይህ ዕድል ውጤታማ እንዲሆን ከማን ምን ይጠበቃል አንሳተፍም ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎችን በተመለከተ የመንግሥት አቋም ምንድን ነው?
☑መልካም አስተዳደር ከማስፈን እና ብልሹ አሰራሮችን ከማረም አኳያ ከመንግሥት በኩል በቀጣይ ምን ሥራዎች ይከናወናሉ?
☑7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተለመደው የምርጫ ሂደት ይከናወናል ወይስ በአዲስ መልክ ከሀገራዊ ምክክሩ መጠናቀቅን ተከትሎ በሚወሰዱ ምክረ ሀሳቦች በአዲስ መልክ ነው የሚካሄደው?
☑ቀጣዩ ምርጫ ሰላማዊ እና ተዓማኒ በሆነ መልኩ እንዲደረግ ምን እየተሰራ ነው? ከሕዝቡስ ምን ይጠበቃል?
☑የባህር በር ፍላጎታችን ከጎረቤታችን ኤርትራ ጋር ባለው ግንኙነት አውድ ውስጥ እንዴት ይታያል? በመንግሥት በኩል ለወንድም የአፍሪካ ሀገራት የማብራራት ሂደቱ ምን ይመስላል የሚለው ቢብራራ?
☑የትምህርት ጥራት ችግርን ለመፍታት እና የተማሪዎችን የማለፍ ምጣኔ ለመጨመር ምን እየተሰራ ነው?
☑የማዕድን ዘርፍ ፕሮጀክቶችን በመገንባት የተጀመሩ ሥራዎችን ማስፋፋት ላይ ምን ተግባራት እየተከናወኑ ነው?