Search

በአዳማ ከተማ በሕዝብ ተሳትፎ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ለአገልግሎት ክፍት ተደረጉ

ረቡዕ ጥቅምት 19, 2018 59

የኮሪደር ልማቱ የኮንፈረስ ከተማ የሆነችውን አዳማን ውብ ገጽታ ከማላበሱ ባለፈ፣ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች ታሳቢ ያደረገ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ኃይሉ ጀልዱ ገልጸዋል።
ልማቱ እውን ሊሆን የቻለው በላቀ የሕዝብ ተሳትፎ ነው ያሉት ከንቲባው፤ የተገነቡትን መሠረተ ልማቶች መጠበቅ እና መንከባከብ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በቀጣይም ከተማዋን ውብ እና ተመራጭ፣ ለነዋሪዎቿም ምቹ እና ተስማሚ እንድትሆን እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
የኮሪደር ልማቱ የተለያዩ የመዝናኛ ስፍራዎች፣ የብስክሌት መንገዶች እና መጸዳጃዎችን ያካተተ ሲሆን፣ እነዚህም ለከተማዋ ነዋሪዎች ምቹ ተደርገው መሠራታቸው ተገልጿል።
የከተማዋ ነዋሪዎች በበኩላቸው የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ልዩ ውበት እዳጎናጸፋት ገልጸው፤ የተገነቡ መሠረተ ልማቶችን መጠበቅ ደግሞ የእኛ ኃላፊነት ነው ብለዋል።
በሰናይት ብርሃኔ