Search

ጣና ነሽ ፪ ጀልባ መደበኛ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ጀመረች

ዓርብ ኅዳር 19, 2018 41

ጣና ነሽ ጀልባ የመጀመሪያውን የመንገደኞች ማጓጓዝ ከባሕር ዳር ወደ ደልጊ እና ደቅ በማድረግ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ጀምራለች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (/) ጣና ነሽ ጀልባን በጎርጎራ ሥራ አስጀምረው ወደ አገልግሎት መግባቷ የሚታወስ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ጣና ነሽ ጀልባ “የጣና ውሃን እየቀዘፈች ባሕር ዳር ከተማን ከጎርጎራ ሎጅ ማገናኘት ጀምራለች” ማለታቸውም ይታወሳል።

188 ተሳፋሪዎችን የማጓጓዝ አቅም ያላት ጣናነሽ አስደማሚው የጣናይቅ የተፈጥሮ ከባቢ የሚደረገውን ጉብኝት እና ወደ ጎርጎራ ሎጅ የሚደረገውን ጉዞ ይበልጥ ምቹ አድርጋው ሰንብታለች።

አሁን ደግሞ ጣና ነሽ ጀልባ የመጀመሪያውን የመንገደኞች ማጓጓዝ ከባሕር ዳር ወደ ደልጊ እና ደቅ በማድረግ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ጀምራለች።

በሳሙኤል ወርቃየሁ

#ebcdotstream #bahirdar #tananeshII #ጣናነሽ፪