Search

ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ፓርቲ ሕጋዊ እውቅና ተሰጠው

ማክሰኞ ኅዳር 30, 2018 307

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ“ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት)" ሕጋዊ የክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት ሰጠ።
ቦርዱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ በዐዋጁ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ለ“ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት)" ሕጋዊ የክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲነት ማረጋገጫ የምሥክር ወረቀት ኅዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም መስጠቱን አስታውቋል።